Catalog
Browse the titles currently available from this author and choose the edition that fits how you want to read.
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የደረሱት መጽሐፍት ከሃምሳ በላይ ይሆናሉ፡፡ በስም የሚታወቁት ግን ሰዓታት ዘመዓልት ወዘሌሊት፣ ኖኅተ ብርሃን ከመጽሐፈ አርጋኖን ጋር አብሮ ታትሟል፣ ውዳሴ መስቀል፣ ቅዳሴ፣ ውዳሴ ሐዋርያት፣ አርጋኖነ ውዳሴ፣ ፍካሬ ሃይማኖት፣ መጽሐፈ ምሥጢር፣ ውዳሴ ስብሐት፣ እንዚራ ስብሐት፣ ሕይወተ ማርያም፣ ተአምኖ ቅዱሳን፣ መጽሐፈ ብርሃን እንዲሁም ጸሎት ዘቤት ናቸው፡፡ አባ ጊዮርጊስ እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ሀብተ መንፈስ ቅዱስ የተሞሉ አባት ናቸው፡፡
በዜማ ትምህርት በጣም ጠልቀው ያውቁ፣ የቅዱስ ያሬድን ዜማ በተለይም ድጓውን በዘመናት ከፋፍለው እና በየበዓላቱ አደራጅተው፣ ቅርጽ በማያስያዝ ለቅዱሳኑ ሁሉ በየባህሎታቸው የሚዜመውን አዘጋጅተው ለደቀ መዛሙራቶቻቸው በማስተማር እንዲስፋፋ አድርገዋል፡፡
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ድጓውን በደብር ነጎድጓድ ሐይቅ ለሰባት ፯ ‹በርእስ አድባራት ተድባበ ማርያም› አስተምረዋል፡፡ በዜማው በኩል አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ከያሬድ በኋላ የተነሡ ዳግማዊ ያሬድ ሲባሉ በዘመኑ የነበሩትን መናፍቃንን በመከራከርና አስተምረው በመርታታቸው ‹ኢትዮጵያዊው ቄርሎስ› የሚል ስምም ተሰጥታቸዋል፡፡ አባ ጊዮርጊስ ስለ ሰማይ፣ ስለ መብረቅና ስለ ዝናም አፈጣጠርና ባሕርያት በሚገባ አስተምረዋል፡፡ ሆኖም ግን ድርሰቶቻቸውን የውጭ አንብባቢዎች ሲጠቀሙበት የሀገራችን ሰዎች ግን የታላቁን ቅዱስ ታሪክ እንኳን በቅጡ የማያውቅ ነው፡፡ እርሳቸው ግን የቤተ ክርስቲያን መብራት ናቸው፡፡ ምክንያቱም ዛሬ በቅዳሴው፣ በማኅሌቱ፣ በሰዓታቱ፣ በምሥጢሩና የምስጋና ድርሰቶች አሁንም ቤተ ክርስቲያን እየተጠቀመችባቸው ትገኛለች፡፡ ይህ ሕሙም ትውልድ መድኃኒት ያስፈልገዋለና መድኃኒቱን ለማግኘት ሌት ከቀን በመጾም፣ በመጸለይና መትጋት እንዳለበት በአጽንዖት አስተምረዋል፡፡አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በአጼ ይስሐቅ ዘመነ መንግሥትም ‹‹ከፍተኛ የቤተ ክርስቲያን ተጠያቂ ሊቅ›› ተደርገው ተሹመው ነበር፡፡
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የትሕት፣ የርኅራኄና የምሥጢር ባለቤት አባት ናቸው፡፡ የርኅራኄ አባት ያልንበት ምክንያት እንዲህ ነው፤ በአንድ ወቅት ሳያመነኩሱ ገና ንጉሥ ዳዊት ልጃቸውን እንዲያገቡና በእርሳቸው ቦታ እንዲተከቱ በተደጋጋሚ ጥያቄ አቀረቡላቸው፡፡ እርሳቸውም የንጉሡን መልክእት በመስማትና ያሞክሮ ልብስ በመልበስ የመጣባቸውን ፈተና አልፈውታል፡፡ በዚህ ምክንያት ንጉሥ ዳዊት ስላልሰሟቸው ብዙ መከራና ሥቃይ አድርሰውባቸዋል፡፡ ግን እኚህ ንጉሥ መስቀሉን ሊያመጡ ሲሄዱ ጎዳና ላይ በቅሎ ረግጣቸው ሞቱ። አባ ጊዮርጊስም የንጉሡን ሞት በሰሙ ጊዜ ስቅስቅ ብለው አለቀሱ፡፡ ‹‹ምነው ያ ሲያንገላታህ፣ ብዙ መከራ ሲያደርስብህና በጨለማ ቤት ሲወረውርህ ደስ ሊል ይገባል እንጂ እንዴት ታለቅሳለህ?›› ብሎ ሰዎች ሲጠይቋቸው ‹‹እንደዚያም ቢሆን ንጉሡ እመቤታችንን ይወዱ ስለነበረ ነው ያዘንኩት›› ብለው መልሰውላቸዋል፡፡ በመጽሐፍ ‹‹የእግዚብሔር መንገድ ቅን ነው። ጻድቃን ይሄዱበታል፡፡ ሕግ ተላላፊዎች ግን ይወድቁበታል፤›› ተብሏል፡፡ (ሆሴ.፲፬፥፱)
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተወለዱ በ፷ ዓመታቸው ኢትዮጵያ አበቅቴ አልቦ በሆነበት ጊዜ ጥንተ ዮን በወንጌላዊው ማቴዎች ዘመን ረቡዕ ቀን ይስሐቅ በነገሥ በዐሥራ አንድ ዓመት በ፲፬፻፰ ሐምሌ ፯ ቀን ዐርፈዋል፡፡
የጻድቁ በረከት በሁላችን ላይ ይደርብን፤ አሜን፡፡
source: https://eotcmk.org/a/አባ-ጊዮርጊስ-ዘጋስጫ